አዲስ ዘመን ሐሙስ ህዳር 25 ቀን
2018 ዓ.ም
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የሌቃ ዱላቻ ፋይናንስ ጽ ቤት ለወረዳው መንገድና ሎጂስቲክስ ጽ/ቤት በወረዳው ካፒታል በጀት መንገድ ጥገና ስራ ለማሰራት የሚውሉ የግሬደር፣ የኤክስካቫተር፣ ሮለር፣ ሲኖ ትራክ እና ሻወር ትራክ ማሽኖችን በኪራይ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የማሽነሪ ኪራይ ፈቃድ ያላችሁና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ በጨረታው እንድትሳተፉ እናስታውቃለን፡፡
አስፈላጊ መስፈርቶች
1. የማሽነሪ ኪራይ ንግድ ፈቃድ የ2018 ዓ.ም የታደሰ
2. የግብር ከፋይ መሊያ ቁጥር (TN Number) ያላችሁና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆናችሁ
3 የ2017/18 ዓ.ም ግብር መክፈላችሁን የሚገልጽ ከገቢዎች ባለስልጣን የሚቀርብ ደብዳቤ
4. ተጫራቾች የማሽኖቹን የምርት ስም፣ የተመረተበትን ሀገር፣ የሞዴል ቁጥር እና የተመረተበትን ዓመት በግልጽ በመጻፍ ማቅረብ አለባቸው::
5. በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገበ መሆን
6. ለመንገድ ጥገና የሚውሉ ማሽኖች ዝርዝር፡-
I. ግሬደር ሞዴሉ 140H/K/G እና የፈረስ ጉልበቱ 185 እና በላይ የሆነ፣ የምርት ዓመቱ ከ2017 ዓ.ም በፊት ያልሆነ፡፡
II. ኤክስካቫተር ሞዴሉ CLDL 325 እና በላይ የሆነ እና የፈረስ ጉልበቱ 38 እና በላይ የሆነ፣ የምርት ዓመቱ ከ2017 ዓ.ም በፊት ያልሆነ፡፡
III. ሲኖ ትራክ ሞዴሉ 325 እና በላይ የሆነ፣ የፈረስ ጉልበቱ 336 እና በላይ የሆነ፣ የምርት ዓመቱ ከ2020 ዓ.ም በፊት ያልሆነ፣ ክፍያው እንደ ርቀቱ (05 ኪ.ሜ, 5-10 ኪ.ሜ, 10-15 ኪ.ሜ እና 15-20 ኪ.ሜ) የሚከፈል ሲሆን
ተጫራቾች ዋጋውን በዝርዝር መግለጽ አለባቸው።
IV. ሮለር ሞዴሉ BW 14 AD እና ከዚህ በታች ያልሆነ የፈረስ ጉልበቱ 16 እና በላይ የሆነ
V. ሻወር ትራክ ሞዴሉ 325 እና በላይ የሆነ የፈረስ ጉልበቱ 336 እና በላይ የሆነ የምርት አመቱ 2017 G.C እና
ከዚህ በፊት ያልሆነ።
7. የባለቤትነት ማረጋገጫ (ሊብሬ) ማቅረብ የሚችል እና ማሽኑ ጉዳት ከደረሰበት በራሱ ወጪ በአስር (10) ቀናት ውስጥ መጠገን ወይም ተመሳሳይ ማሽን መተካት የሚችል፡፡
8. የኪራይ ቦታ አድራሻ በአግባቡ የተረጋገጠ የወረዳ፣ ቀበሌ፣ የቤት ቁጥር እና ስልክ ቁጥር ማቅረብ አለበት።
9. ተጫራቾች የዚህን ስራ ልምድ የሚያሳይ ማስረጃ ከ2015 ዓ.ም በፊት ማቅረብ አለባቸው (አዲስ ፈቃድ አይታሰብም)።
10. ተጫራቾች እንደ ምግብና መጠጥ፣ ማረፊያ ቦታ፣ ማሽኑን በስራ ቦታ መጠበቅ፣ ነዳጅ እና ሌሎች ወጪዎችን በራሳቸው ይሸፍናሉ።
11. የማሽኖቹን የትራንስፖርት ወጪ (መጫንና ማውረድ) ተጫራቾች በራሳቸው ይሸፍናሉ፡፡
12. ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ የሚችል ሲሆን የጨረታው አሸናፊ ከተለየ በኋላ በአምስት (5) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን ተጫራቹ የድርጅቱን ስነ-
ምግባር ካላከበረ የጨረታ ማስከበሪያው ያለ ምንም ጥያቄ ለመ/ቤቱ ገቢ ይሆናል፡፡ እንዲሁም አሸናፊው
ማሸነፉን ካወቀ በኋላ ማሽኑን በተስማማበት ጊዜ ካላቀረበ የጨረታ ማስከበሪያው እና የውል ማስከበሪያው ለመ/ቤቱ ገቢ ይሆናል፡፡
13 የውል ማስከበሪያው ከጠቅላላው ዋጋ 10% የሚያስይዝ ሲሆን የውል ማስከበሪያው ስራው ከተጠናቀቀ በኋላ
ተረጋግጦ ርክክቡ ከተፈጸመ በኋላ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
14. የጨረታው አሸናፊ በአካል ቀርቦ ውል መፈረም አለበት።
15. ተጫራቾች ለጨረታው የሚያስፈልገውን ሰነድ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) ብቻ ለወረዳ ሌቃ ዱላቻ ገቢዎች ጽ/ቤት የማይመለስ ክፍያ በመክፈል ከፋይናንስ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ከፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
16. የመንገድ ጥገናው ጥራት ያለው እንዲሆን መንገድና ሎጂስቲክስ ጽ/ቤት ወይም የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት በመከታተል የማስቆም መብት አለው።፡
17.ለጨረታ የሚቀርብ ማንኛውም ሰነድ የተሰረዘ፣ የደፈረሰ ወይም ፎቶ ኮፒው የማይነበብ ከሆነ ከጨረታው ውጪ ይሆናል፡፡
18. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በአራት (4) ፖስታዎች ማቅረብ አለባቸው፡፡
A. የቴክኒክ ፖስታ ዋናውና ኮፒው ለየብቻ በካኪ ፖስታ ተደርጎ በድርጅቱ ማህተም ተረጋግጦ በሁሉም ፖስታዎች ላይ ፊርማ ተደርጎ በአንድ ፖስታ መቅረብ አለበት።
B. የፋይናንስ ፖስታ ዋናውና ኮፒው ለየብቻ በካኪ ፖስታ ተደርጎ በድርጅቱ ማህተም ተረጋግጦ በሁሉም ፖስታዎች ላይ ፊርማ ተደርጎ በአንድ ፖስታ መቅረብ አለበት።
C. ሁሉም (የቴክኒክና የፋይናንስ ፖስታ) በአንድ ትልቅ ፖስታ ተደርጎ በድርጅቱ ማህተምና ፊርማ ተረጋግጦ በግዢ
ክፍል መመዝገብና በግዢ ክፍል ውስጥ በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
19. ይህ ጨረታ ለ21 የስራ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ23/4/2018 ዓ.ም በ4:00 ሰዓት ላይ የሚዘጋ
ሲሆን በዚሁ ቀን ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በወረዳ ም/አስተዳደር ክፍል በ 4:30 ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች ሰነዳቸውን ካስገቡ በኋላ በጨረታው መክፈቻ ላይ ባይገኙም የጨረታውን ሂደት
ኢያስተጓጉልም።
ማሳሰቢያ:
- ድርጅቱ የተሻለ ዋጋ ወይም ሌላ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ
የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች በጨረታ መክፈቻ ላይ ባይገኙም ጨረታውን ከመከፈት አያስተጓጉልም።
- ሁሉም ፖስታዎች የድርጅቱን ስምና ስልክ ቁጥር መያዝ አለባቸው።
- ለተጨማሪ መረጃ በ0935886718/0920410808/0934392199 ስልክ ቁጥር መጠየቅ ይቻላል፡፡
በወረዳው ካፒታል በጀት የተሸፈኑ የማሽኖች ኪራይ ዋጋ
ተ.ቁ የማሽኑ ዓይነት መለኪያ ብዛት የአንድ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ -
1 ግሬደር ሰዓት 150
2 ኤክስካቫተር ሰዓት 150
3 ሻወር ትራክ ሰዓት 70
4 ሮለር ሰዓት 100
ጠቅላላ ዋጋ
ተ.እታ (5%)
ተ.እታን ጨምሮ ጠቅላላ ዋጋ
በወረዳው ካፒታል በጀት የተሸፈኑ የሲኖ ትራክ ኪራይ ዋጋ
ተ.ቁ የማሽኑ ዓይነት መለኪያ የጊዜ ልዩነት በኪሜ ብዛት የአንድ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ
1 ጭነት መኪና (D/truck) ባጆ 0‐5ኪ.ሜ 250
5-10ኪሜ
10-15ኪ.ሜ
15-20ኪ.ሜ
በምስራቅ ወለጋ ዞን የሌቃ ዱላቻ ፋይናንስ ጽ/ቤት