አዲስ ዘመን ሰኞ ጥር 11 ቀን 2018ዓ.ም
ሁለተኛ ዙር የጨረታ ማስታወቂያ 002/2018
በጉለሌ ክ/ከተማ
ወረዳ 05 የጀኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ 2018 ከመደበኛ በጀትና ከዉስጥ ገቢ በጀት አገልግሎት የሚውል
ሎት 1 አላቂ የቢሮ ዕቃዎች እና የትምህርት መሳሪያዎች፣ ሎት 2 ቋሚ የፈርኒቸር ዕቃዎች ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ፣ ሎት
4 የደንብ ልብስ ስፌት እና ሎት 5 ኤሌክትሮኒክስ ጥገና ሁለተኛ ዙር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ሰለሚፈልግ ተጫራቾች ከዚህ
ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርት ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. በዘርፉ
የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው። ተጫራቾች ይህንኑ የሚገልፅ ማስረጃ ዋናውንና
ፎቶ ኮፒውን ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. ተጫራቾች
የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በጉለሌ/ክ/ከተማ ወረዳ 05 ከዊንጌት ወደ አስኮ
በሚወሰደው መንገድ ካዎ ጄጄ የምግብ ማምረቻ ኮምፕሌክስ ቀጥሎ በሚገኘው የጄኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አዲሱ
ህንፃ ቢሮ ቁጥር 6 የማይመለስ በየሎቱ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ሰነዱ መውሰድ ይችላሉ በተጨማሪም ሰነድ የገዙበትን
ደረሰኝ ኮፒ ከሰነዱ ጋር አያይዘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
3. ተጫራቾች
የሚያቀርቡትን ዕቃ ጥራት ያለው ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑ ናሙና ማቅረብ ባለባቸው ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች
የዕቃዎች ዝርዝር እና የጨረታ ማወዳደሪያ ሰነድ ላይ ስማችሁን በመፃፍ ፈርማችሁ አድራሻችሁን ማስፈርና እንደ ሚታይ አርጋችው ማህተም በማድረግ ማስታወቂያ
ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ከዊንጌት ወደ አስኮ በሚወሰደው መንገድ ካዎ
ጄጄ የምግብ ማምረቻ ኮምፕሌክስ ቀጥሎ በሚገኘው የጄኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2 ደረጃ ት/ቤት አዲሱ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 106 ለጨረታው
በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ስታስገቡ ከሙሉ ፋይል ኦርጅናል እና ኮፒ ሰነድ ጋር እስከ በ10 ኛው ቀን 11:00 ሰዓት ድረስ ማስገባት
ይኖርባቸዋል፡፡
5. ጨረታው
ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማስታወቂያው በወጣበት በ 11 ኛው ቀን በ 4፡30 በጀኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ
2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 6 ይከፈታል። የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም በበዓል ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የስራ
ቀን በተገለፀው ሰዓት ይከፈታል፡፡
6. ጨረታው
ከተከፈተ በኃላ ተጫራቾች በሰነድ የሰጡት ዋጋ መለወጥ መሻሻል ወይም ከውድድሩ እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
7. የመወዳደሪያ
ዋጋ ከቫት ጋር መሞላት አለበት፡፡
8.ተጫራቾች
የጨረታው ማስከበርያ ለሎት 1 ብር 3,000 (ሶስት ሺህ ብር ብቻ ለሎት 2 ብር 5,000 (አምስት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት 3 ብር
4,000 (አራት ሺህ ብር ብቻ) ለሎት 4 ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር ብቻ) ለሎት 5 ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር ብቻ)
በባንክ በተመሰከረለት CPO ማስያዝ ይኖርባችዋል፡፡
9. ት/ቤቱ
እንደ አስፈላጊነቱ የዕቃውን ብዛት ከውል በፊት 20% መጨመር ወይም መቀነስ ይችላል፡፡
10. አሸናፊው
ድርጀት ዕቃዎቹን እስከ ጀኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ በራሱ ትራንስፖርት አጠቃሎ ማስገባት
አለበት፡፡
11. በጥቃቅንና
አነስተኛ ለተደራጃችሁ መወዳደር የምትችሉት በረታችሁት ምርት ወይም እሴት በጨመራችሁት ብቻ ሲሆን ከዚህ ዉጪ ግን እንደ ማንኛዉም
እጩ ተወዳዳሪ የጨረታ ሰነድ መግዛትና የውል ማስከበሪያ ሲ ፒ ኦ (CPO) በማስያዝ መወዳደር የምትችሉ ይሆናል፡፡
12 ተጫራቾች
ዕቃውን እስከ 6 ወር 25 % ባስገቡበት ዋጋ መስሪያቤቱ ለመጨመር ቢጠይቅ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
13. ሰነዱ
ላይ ሰርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ካለበት ውድቅ ይሆናል፡፡
14. መስሪያ
ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በስልክ ቁጥር +251112804292,+2512795495,0989066757 በጉለሌ/ክ/ ከተማ ወረዳ 05 ከዊንጌት ወዳ አሰኮ በሚወሰደው
መንገድ ካዎ ጄጄ የምግብ ማምረቻ ኮምፕሌክስ ቀጥሎ በሚገኘዉ ጄኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2 ደረጃ ት/ቤት አዲሱ ህንፃ
በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 05 የጀኔራል ታደሰ ብሩ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት